Wednesday, September 11, 2013

አዳም ከኤዶም ገነት የተባረረው ለምንድን ነው?

በሁሉም አካባቢ ለምትገኙ የፌስቡክ ጓደኞቼ በመጀመሪያ እንኳን ከዘመነ ማቴዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ በሰላም አሸጋራችሁ ዘመኑ የሰላም የፍቅር የመተሳሰብና የሰላም ይሁንላችሁ፡፡
አሮጌ አመት አልፎ አዲስ ዘመን ሲመጣ ሁሉም ሰው በአዲስ ሀሳብ በአዲስ እቅድ ዘመኑን ለመቀላቀል ይወስናል በአመቱ ውስጥ ሊሰራቸው የሚፈልጋቸውን ሥራዎች ይነድፋል እንዲከናወኑለት ይፀልያል ለተግራዊነታቸውም ቃል ይገባል፡፡
ምን ያህሉ ባለመውና ባቀደው በነደፈው እቅድ እንደሚመራ ልብ ይቁጠረው፡፡
ከብዙ የፌስቡክ ጓደኞቼ ጋር በውስጥ ገጽ ብዙ እናወራለን እንመካከራለን ጥያቄና መልሶችንም እንለዋወጣለን፡፡ ታዲያ እነዚህ ጓደኞቼ ጥያቆዎቻችንን ለምን በፊት ገጽ አናደርጋቸውም ምንአልባት እኮ አንድ ሰው ሊማርባቸው ይችላል ብለውኝም ነበር በዚህም የተነሳ መ/ር ሰሎሞን ፋንቱ የምትል ገጽ ከፈትኩና እሁን ብዕራቸው ያማረ ምክራቸው የሰመረ ትምህርታቸው የጠነከረ ብዙ ፀሐፊዎች ባሉበት አሁን እኔ? ብዬ ተውኩት ጥቂቶች ታዲያ የያዘውን የወረወረ እኮ ብለው ስላሉኝ በዚህ ዓመት እኔስ ለምን የምችለውን ያክል ለመጻፍ አልሞክርም ብዬ አቀድኩ ወሰንኩም የመጀመሪያውን ሃሳብ በማንሳትም እቅዴን አንድ ብዬ ተግባራዊ አደረኩ እግዚአብሔር ይርዳኝ፡፡
እኔ ለጥያቄዎች መልስ ለመስጠት  ለመምከርና ለመጻፍ ስነሳ በዚህ የመጻፊያ መሳሪያ ከሚጽፉ ወንድሞቼ የተሻለ እውቀት ኖሮኝ የእውቀት ክፍተታቸውን ለመሙላት አይደለም ይልቁንም የሥራ ፀባዬ ከዚህ የመጻፊያ መሳሪያ ጋር የተገናኘ በመሆኑ የግዜ ክፍተታቸውን ሊሞላ ይችል ይሆናል፡፡
በዚህ ዓመት የመጀመሪያ ዓመትና የመጀመሪያ የመነሻ ሃሳብ የመጀመሪያዉን ሰው ብናደገውስ  
በጥያቄ ልነሳና የብዙዎቻችሁን መልስ ካየሁ በኋላ ታናሻችሁ የምሆን እኔ ደሞ ሃሳቤን ገልጣለሁ
አዳም ከኤዶም ገነት የተባረረው ለምንድን ነው?

ምክንያታዊ መልስ እፈልጋለሁ አደራችሁን ጥያቄዬን እንዳትንቋን ምናልባት መልሱን ካገኛችት . . . . . ሁላችሁም ተሳተፉበት


No comments:

Post a Comment