ሞት
ምን ምን ይሸታል አንዳንዴ ሰዎች ሞት ሞት ሸቶኛል ሲሉ እንሰማቸዋለን ምን ምን ሸቷቸው ይሆን፡፡
ሞት
በቁሙ የህግ መተላለፍ ቅጣት የሀጢአት ውጤት ነው፡፡
በስጋዊ
አፍንጫችን ስናሸት ለሚሸተተው ነገር በወጣለት እና በተሰጠው ህግ/ማንነት/ ብቻ እናሸተዋላን ወደ አፍንጫችን የሚገባው ሽታ መጥፎ
መአዛ ካለው ይህ ሉሁሉም ሰው መጥፎ መአዛ ነው መልካም መአዛ ከሆነ ደሞ ለሁሉም ሰው መልካም መአዛ ነው፡፡ ከአንድ ኩሬ በአንድ
ግዜ መራራና ጣፋጭ እንደማይቀዳ ሁሉ ማለት ነው፡፡ ይህ የስጋዊ አፍንጫችን እውነት ነው፡፡
በመንፈሳዊ
ህይወት ግን እንዲህ አይደለም ከአንድ ነገር ላይ በማመን እና ባለማመን የህይወትን አና የሞትን ሽታ እናሸታለን
የሀዋርያው
ጳውሎስን መልዕክት ስናነብ የምናገኘው እውነት ይህንን ያስረግጥልናል
በሚድኑትና በሚጠፉት ዘንድ ለእግዚአብሔር የክርስቶስ መዓዛ ነን፤ለእነዚህ ለሞት
የሚሆን የሞት ሽታ ለእነዚያ ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን፡፡ 2ቆሮ 2፤15
ጳውሎስ
አንድ ነው ደቀ መዛሙርቱም እንደዚሁ፤ ነገር ግን የክርስቶስ መዓዛ ሲሆኑ ሁለት መዓዛ አላቸው የሞትና የሕይወት ሽታ፡፡ ቃላቸውን
ለሚሰሙትና ለሚድኑት ለሕይወት
የሚሆን የሕይወት ሽታ ለማያምኑባቸው
ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ፡፡
የሐዋርያትን
የአገልግሎት ዘመን ስንመለከት ልዩነቱ ገና ከመንፈስ ቅዱስ መውረድ ቀን ጀምሮ ይጀምራል፡፡ የሐዋ.ሥ 2፤4 በሁሉም መንፈስ ቅዱስ
ሞላባቸው መንፈስም ይናገሩት ዘንድ እንደሰጣቸው በሌላ ልሳኖች ይናገሩ ጀመር፡፡ በሌላ ልኖችም ሲናገሩ የሚናገሩት ግስና ባለቤት
ያለው ቋንቋ ስነበር ሁሉም በየራሳቸው ቋንቋ ሲናገሩ ይሰሙዋቸው ነበር በዚህም ተደነቁ ይህንን ያደረገውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ
በዛችም እለት ከቅዱስ ጴጥሮስ ትምህርት የተነሳ ሦሥት ሺህ ነፍሳት አመኑ፡፡
በተቃራኒውግን
በዚሁ ምእራፍ ቁጥር 13 ላይ ሌሎች ግን እየፌዙባቸው፡፡ ጉሽ የወይን ጠጅ ጠጥተዋል አሉ፡፡ የሚል ቃል እናገኛለን ከአንዱ የክርስቶስ
መአዛ ላይ ሞትና ሕይወት ማሽተት እንዲህ ነው፡፡
ሉቃስ
7፤23 በእኔ የማይሰናከል ብፁዕ ነው፡፡
ኢየሱስ
ክርስቶስ ወደዚህ ምድር ሲመጣ ለሁለት ነገር እንደመጣ ደጋግሞ ሲያስተምር እንደነበር ወንጌል ይነግረናል አንድም ለሞት አንድም ለሕይወት፡፡ ለዚህም ነው በእኔ የማይሰናከል ብፁዕ ነው፡፡ ያለው
ማቴ
10፣34
በምድር
ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልጣሁም፡፡ ሰውን ከአባቱ፤ሴት ልጅንም ከእናትዋ ምራትንም
ከአማትዋ እለይ ዘንድ መጥቻለሁ፡፡
ዮሐ
9፤39 ኢየሱስም፡፡ የማያዩ እንዲያዩ የሚያዩ እንዲታወሩ እኔ ወደዚህ ዓለም ለፍርድ መጥቻለሁ፡፡
ሉቃ
2፤34-35 ይህ በእስራኤል ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፤
እነዚህን
እና እነዚህን የመሳሰሉት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የሚነግሩን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚጠፉትና በሚድኑት መካከል የሕይወትና የሞት መዓዛ/ሽታ/ እንደሆነ ነው፡፡
በክርሰቶስ
የማያምኑትን አህዛብን አንኳን ትተን አንድ መጽሐፍ ቅዱስ እያነበብን አንድ ጌታ ኢየሱስን እናመልካለን የምንል ህዝቦችን እንኳን
ብንመለከት እጅግ ብዙ ቦታ ተሰነጣጥቀን ብዙ ቤተ እምነቶችን አቋቁመን እንታያለን፡፡
በነዚህ
ቤተ እምነቶች ሁሉ ክርስቶስ የሚሰበክ ቢመስልም ሥሙ እየተጠራ ተአምራት
የሚደረግ ቢመስልም ሁሉም ከክርስቶስ መልካሙንና የሕይወት መአዛ አሽቶአል ማት አይቻልም፡፡ ምክንያቱም
በኢየሱስ
ክርስቶስን ማመን ስሙን መጥራት በስሙ ተአምራትን ማድረግ ጭምር በራሱ
ብቻ የክርስቶስ መሆንን አያመለክትም፡፡ ቃሉ እንዲህ ይላልና፡፡
ማቴ
7፤21 በሰማይ ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆን ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግስተ ሰማያት የሚገባ አይደለም፡፡
ቁጥር 23 ከቶ አላውቃችሁም፤እናንተ አመፀኞች ከእኔ እራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ፡፡
ክርስቶስ
በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ ሁልት ሽፍቶች አንዱ በቀኝ ሌላው በግራ ተሰቅለው ነበር ሁለቱም ክርስቶስን ከግራና ከቀኝ እኩል ያዩትም
ነበር፡፡ ነገር ግን ከክርስቶስ ላይ አንዱ ሕይወትን ሌላኛው ሞትን ያሸቱ ነበር፡፡ ዛሬም በስሙ እናምናለን የምንል ሁላችን እንዲሁ ክርስቶስ በቀራንዬ በመስቀል በተሰቀለ ጊዜ ከግራና ከቀኙ
እንደተሰቀሉት ሁለት ሽፍቶች በሁለት አቅጣጫ እናየዋለን አንዳችን ለሕይወት ሌላችን ለሞት ክርስቶስ ለአንዳችን
ለህይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ለአንዳችን ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ነው፡፡
2ነገ
3-22 ላይ የሞአብ ንጉስ የሞሳ እና የአክአብ ልጅ የኢዮራም ታሪክ ከዚህ ጋር ተመሳሳይነት ስላለው እዚህጋ እናንሳው
የሞአብ
ንጉስ ሞሳ ለእስራኤል ንጉስ አክአብ ከበጎች ጠጉር ግብር ይገብር ነበር ነገር ግን ንጉሱ አክአብ ሞቶ ሊጁ ኢዮራም በተተካ ግዜ
ግን ንጉስ ሞሳ አልገብርም ብሎ አመጸ በዚህ ግዜ ንጉስ ኢዮራም የይሁዳ ንጉስ ኢዮሳፍጥን እና የኤዶምያስን ንጉስ አስከትሎ ወደ
ሞአብ ዘመተ በኤዶምያ በረሃ ሰባት ቀን ከተጓዙ በኋላ ግን ውሃ ጠፋ ሶስቱ ነገስታትም ተጨነቁ እግዚአብሔር ግን በነቢዩ ኤልሳዕ እንዲህ አላቸው ንፋት አታዩም ደመናም አታዩም
እግዚአብሔር ግን ይህንን ሸለቆ በውሃ ይሚላል ይህም በእግዚአብሔር አይን ፊት ቀላ ነው አላቸው፡፡ በማግስቱም ሸለቆውን ውሀ ሞላው
ለሦሥቱ ነገስታትም የሕይወት ውሃ ሆነላቸው፡፡ በማለዳም ሞአባውያን
ሶስቱ ነገስታት ሊወጓቸው እንደመጡ ሰምተዉ በተራራ ላይ ተከማቹ በማለዳም ሲመለከቱ ውሀው ደም መስሎ ታያቸው እንዲህም አሉ ሦስቱ
ነገስታት እርስ በርሳቸው ተዋግተዋል ደማቸውም ይኸው እንግዲህ ሞአብ ሆይ ለምርኮ እንውረድ ብለው ወረዱ ሦስቱ ነገስታትም ከተማቸውን
እስኪያጠፉ ድረስ መቷቸው፡፡ ይለናል ታሪኩ
በኤዶምያስን
ሸለቆ የሞላው ውሃ አንድ ውሃ ነው ነገር ግን እስራኤል በዚህ ሞአባውያን ከዚያ ሆነው ሲያዩት ግን ልክ ክርስቶስን በሁለት አቅጣጫ
በመስቀል ላይ ሲያዩት እንደነበሩ ሁለት ሽፍቶች ሕይወትና ሞት አሸተቱበት፡፡
ደቀመዛሙርቱ
ቅዱሳኑ
መላእክቱ
ድንግል
ማርያም
ቤተ
ክርስቲያን
በሚጠፉትና
በሚድኑት መካከል ለእግዚአብሔር የክርስቶስ በዓዛዎች ናቸው፡፡ ለነዚህ ለህይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ለነዚያ ለሞት የሚሆን
የሞት ሽታ
እኛስ
ከዚህ ምን ሸቶን ይሆን ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ወይስ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ
ወስብሐት
ለእግዚአብሔር
መ/ር
ሰሎሞን ፋንቱ
