ረቡዕ ማታ በብሔራዊ ቴያትር የቴዎድሮስ ትዝታ የሚል ቴያትር እየታየ ነው፡፡ ያዘጋጀው ጌትነት እንየዉ ይመስለኛል ሱራፌል/የሰው ለሰው ኩራ ሽመልስ አበራ ጆሮና ሌሎችም ይሳተፉበታል፡፡
እንዳየው የጋበዙኝ ሰዎች ከነገሩኝ በላይ ታሪክን የኋሊት የሚያሳይ ቴያትር ሆኖ አገኘሁት በጣም ያምራል፡፡
የዛሬ ሀሳቤ ስለ ታሪኩ ይዘት፣ አወቃቀር፣ የታሪክ ፍሰቱ ለመናገር አይደለም እንደ አንድ ተመልካች በጣም ቆንጆ ሆኖ ቀርቧል ማለት ይበቃኛል፡፡ አዲስ ተቀምጦ ጎንደርን ጋፋትን መቅደላን እንዲያዩ/በህሊናዎ/ የሚያደርግ ሀይል አለው፡፡
ሌላ ያየሁት ነገር ግን ቲያትሩ ከሚጀመርበት ሰዓት በፊት ምናልባትም ከሁለት ሰዓት በፊት ቀድሞ አዳራሹን የሞላው ተመልካች ምን ያክል በተመስጦ ይከታተል እንደነበር በፍቅር አድናቆቱን ይቸር እንደነበር በታሪክ የኋልዮሽ ምልከታ ስሜቱ ሲነካ በጭብጨባ አዳራሹን ያቀልጥ እንደነበር አይቻለሁ፡፡
ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት ስለ ቴያትሩ ይዘት ለመናገር ሙያም መስመርም ይጠይቃልና ቆንጆ ነው እዩት ከማለት ውጭ ምንም ባልል ከብዙ ነገር አመልጣለሁ፡፡
ምንም ካላልክ ለምን . . . ለሚለኝ ግን እኔ ያየሁት ሰው ምን ያክል ታሪክን ማወቅ መስማትና ማየት እንደሚያስደስተው ነው፡፡ አሁን የምናየው ትውልድ ለታሪኩ ለሀገሩ ለሃይማኖቱ ቁብ የሌለው ነው ተብሎ የሚታማውን ያክል መሰረት ከሌለ ቋሚ ግድግዳ ቤት የለም ብሎ የሚያስብም ብዙ እንደሆነ አይቻለሁ፡፡
ታሪክ አሁን ላለንበት ጊዜ መሰረት ይመስለኛል ታሪክ የሌለው ህዝብ ስለማንነቱ የት መጣነቱ መናገር የሚከብደው የማይችል የሚያፍርም ይመስለኛል፡፡
ረዥም ታሪክ የሌላቸው ሀገራት ራሳቸውን ባለታሪክ እንደሆኑ ለማሳመን በብዙ ሲደክሙ ስናይ እኛ በተቃራኒው ሀገሪቱ የታሪክ ሀብታም ሆና ለሀገሩ ለታሪኩ ለቅርሱ ግድ የሌለው ትውልድ እየገነባን መሆኑ ሲታሰብ ምን እየሰራን ነው ያሰኛል፡፡
ከሀያ ዓመት በፊት ይመስለኛል ፔንፓል/የብእር ጓደኛ/ እየተባለ ብዙ ሰው ከውጭ ዜጎች ጋራ ደብዳቤ ይጻጻፍ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ በዚያን ጊዜ እጅግ በጣም የገረመኝ ነገር ነበር አንዱ የማውቀው ሰው ጀርመን ሀገር ካለች የብዕር ወዳጁ ጋር ሲጻጸፍ ስለታሪክ ተነሳና ኢትዮጵያ ባለብዙ ታሪክ ሀገር ነች ለምሳሌ ብሎ ጀርመን የምትባል ሀገር የሌለችበት ነገር ግን ኢትዮጵያ የምትገኝበትን አንድ ካርታ ላከላት ከዚያን ጊዜ በኋላ አልተጻጻፉም ዘጋችው ነው የሚባለው ጥርቅም አድርጋ፡፡
ዛሬ እሷን ሆኜ ሳስበው ታሪካቸው ከኛ ሀገር ታሪክ እኩል ባለመሆኑ ተናዳ ተባሳጭታ ወይም አፍራ መሆን አለበት፡፡
በእንድ ወቅት እግዚአብሔር ከእስራኤል ጋር ቃል ኪዳን በገባበት የቃሌ ኪዳን ታቦት እጅግ ታላላቅ ተአምራትን ያደረገና ይህ በአንድ ወቅት የዓለምን ታሪክ ይመራ የነበረ የቃሌ ኪዳን ታቦት የት እንደሚገኝ የማይታወቅና ያልተረጋገጠ ነው ብለው የሚያምኑ ሀያላን ሀገራት የዚህ ታላቅ ታሪክ እና ቅርስ ባለቤት ለመሆን ዓለምን ሲንጧት እያየን ብዙ ታዝበናል፡፡ ምናልባትም በሀገራችን የጽላት ሽያጭ ለታሪክና ቅርስ ግድ የሌላቸው እና ሆዳቸው አምላካቸው የሆኑ ሰዎችን ተገን በማድረግ በሚደንቅ እና መጠኑ በበዛ ገንዘብ እየተቸበቸበ ያለው ምናልባትም የሙሴ ጽላትን ብናገኝ ብለው እንደሆነ ይታመናል፡፡
ይኽ ሁሉ ሰው ለታሪክ ለሀገርና ለቅርስ ያለውን ስሜት የሚናገር ይመስለኛል፡፡ ሀገርን ታሪክን እና ቅርስን ለመውደድና ለማክበር ምክንያት የሚያስፈልግ አይመስለኝም፡፡
አሁን አሁን ግን የምናያቸው ነገሮች ከዚህ እየወጡ ይመስለኛል፡፡ ትቅልዱ ለታሪኩና ለቅርሱ ግድ እንዳይኖረው የሚሰብኩ ብዙዎች ናቸው፡፡ መንግስትም እንደመንግስት ሰው ለሀገሩ ለቅርሱና ለታሪኩ ግድ እንዲኖረው የሚጠበቅበትን ሁሉ እየሰራ ነው የሚል እምነት የለኝም፡፡ በትምህርት ቤት በዩንቨርሲቲዎች ጭምር የታሪክ ትምህርት ከየ ካሪኩለሙ እየሳሳና እየወጣ ይመስለኛል በአንዳንድ የግል ትምህርት ቤቶች አማርኛ መናገር የወንጀል ያክል እየታየ መምጣቱ የአደባባይ ምስጢር እየሆነ ነው፡፡ ለሀገር ለታክና ለቅርስ ለሃይማኖትም ግድ የሌለውን ትውልድ ሀገር እያፈራች እና እያሳደገች ይመስለኛል፡፡
ወገኔ ስለ ወንጭፍ ወይም ቀስት አስበህ ታውቃለህ ወንጭፍም ሆነ ቀስት ሩቅ የሚሄደው ወደ ኋላ በሚሳበው መጠን ነው፡፡ እድገት ብልጽግናም ዘመናዊነትም እንደዚሁ ይመስሉኛል፡፡ ታሪክን ወደ ኋላ ባየንው በቃኘነው ቁጥር ይመስለኛል ወደ ፊት በሚገባው ፍጥነት መወንጨፍ የምንችለው፡፡ ‹‹የኋላው ከሌለ የለም የፊቱ›› ይባል የለ፡፡
ሕብረተሰቡ በቀና ጎዳና እንዲራመድ ከሚያግዙና ከሚያስተምሩ መንገዶች፣ መድረኮች ወይም ተቋማት መካከል የኪነጥበቡ መድረክ አንዱ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ አሁን በቴዎድሮስ ትዝታ ቴያትር እንዳየሁት አዘጋጁን አደንቃለሁ የጋዙኝን አመሰግናለሁ፡፡
መስመሬ ስላልሆነ በጥልቀት መንካት ባልፈልግም ፊልሞቻችንም ይህንን አርአያ ቢከተሉ እንዴት መልካም ነበር ማለት እፈልጋለሁ፡፡
ብዙ በታሪክ ላይ የሚያጠነጥኑ ፊልሞችን ሳይ እኛ ታሪክ የለንም ወይስ ታሪክን በፊልም መልክ መስራት ለኛ አልተፈቀደም ብዬ እንዳስብ ያደረገኘ ጊዜ አንዴና ሁለት ግዜ ብቻ አይደለም፡፡ አሁን በእኛ ሀገር በቀን አንድ ፊልም መውጣት ጀምሯል የሚል ነገር እንዳነበብኩ አስታውሳለሁ፡፡ ግን ታሪክን የሚያስተምር የሚያሳይ ፊልም ግን እንዳለ መስማቴን እጠራጠራለሁ፡፡ ብዙዎቹ እሁድ በተቀረጹበት ልብስ ሰኞ ካፌ የሚታዩ ቤት ለምነው የሚቀረጹ አሁን ያለንበትን አኗኗር ብቻ የሚያሳዩ መሆናቸውን ሳይ ወደ ኋላ ተመልሰው ፊልም ለመስራት በጊዜው የነበረውን ገጽታ ለመሳል የሚቻልባቸውን ነገሮች ለማዘጋጀት እና ለፊልሙ የሚሆን መንደር ለመገንባት ወጪ ማውጣት የሚፈሩ ወይም የማይፈልጉ ይመስለኛል፡፡
ተመልካች አናገኝም ብለው እንዳይሆን ግን የቴዎድሮስ ትዝታን ተጋፍቶ ከሁለት ሰዓት በፊት ቀድሞ የሚገኝ ተመልካች ሀሳባቸውን ያፈርሰዋል፡፡
ለሀገሩ ለታኩና ለቅርሱ የሚጨነው ትውልድ ፈጣሪ አያሳጣን
ይብቃኝ በድጋሜ በማየቴ ተደስቻለሁ አዘጋጁን አከብራሉ የጋበዙኝን አመሰግናለሁ ያላያችሁትን ጋዣለሁ ሠላም
እንዳየው የጋበዙኝ ሰዎች ከነገሩኝ በላይ ታሪክን የኋሊት የሚያሳይ ቴያትር ሆኖ አገኘሁት በጣም ያምራል፡፡
የዛሬ ሀሳቤ ስለ ታሪኩ ይዘት፣ አወቃቀር፣ የታሪክ ፍሰቱ ለመናገር አይደለም እንደ አንድ ተመልካች በጣም ቆንጆ ሆኖ ቀርቧል ማለት ይበቃኛል፡፡ አዲስ ተቀምጦ ጎንደርን ጋፋትን መቅደላን እንዲያዩ/በህሊናዎ/ የሚያደርግ ሀይል አለው፡፡
ሌላ ያየሁት ነገር ግን ቲያትሩ ከሚጀመርበት ሰዓት በፊት ምናልባትም ከሁለት ሰዓት በፊት ቀድሞ አዳራሹን የሞላው ተመልካች ምን ያክል በተመስጦ ይከታተል እንደነበር በፍቅር አድናቆቱን ይቸር እንደነበር በታሪክ የኋልዮሽ ምልከታ ስሜቱ ሲነካ በጭብጨባ አዳራሹን ያቀልጥ እንደነበር አይቻለሁ፡፡
ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት ስለ ቴያትሩ ይዘት ለመናገር ሙያም መስመርም ይጠይቃልና ቆንጆ ነው እዩት ከማለት ውጭ ምንም ባልል ከብዙ ነገር አመልጣለሁ፡፡
ምንም ካላልክ ለምን . . . ለሚለኝ ግን እኔ ያየሁት ሰው ምን ያክል ታሪክን ማወቅ መስማትና ማየት እንደሚያስደስተው ነው፡፡ አሁን የምናየው ትውልድ ለታሪኩ ለሀገሩ ለሃይማኖቱ ቁብ የሌለው ነው ተብሎ የሚታማውን ያክል መሰረት ከሌለ ቋሚ ግድግዳ ቤት የለም ብሎ የሚያስብም ብዙ እንደሆነ አይቻለሁ፡፡
ታሪክ አሁን ላለንበት ጊዜ መሰረት ይመስለኛል ታሪክ የሌለው ህዝብ ስለማንነቱ የት መጣነቱ መናገር የሚከብደው የማይችል የሚያፍርም ይመስለኛል፡፡
ረዥም ታሪክ የሌላቸው ሀገራት ራሳቸውን ባለታሪክ እንደሆኑ ለማሳመን በብዙ ሲደክሙ ስናይ እኛ በተቃራኒው ሀገሪቱ የታሪክ ሀብታም ሆና ለሀገሩ ለታሪኩ ለቅርሱ ግድ የሌለው ትውልድ እየገነባን መሆኑ ሲታሰብ ምን እየሰራን ነው ያሰኛል፡፡
ከሀያ ዓመት በፊት ይመስለኛል ፔንፓል/የብእር ጓደኛ/ እየተባለ ብዙ ሰው ከውጭ ዜጎች ጋራ ደብዳቤ ይጻጻፍ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ በዚያን ጊዜ እጅግ በጣም የገረመኝ ነገር ነበር አንዱ የማውቀው ሰው ጀርመን ሀገር ካለች የብዕር ወዳጁ ጋር ሲጻጸፍ ስለታሪክ ተነሳና ኢትዮጵያ ባለብዙ ታሪክ ሀገር ነች ለምሳሌ ብሎ ጀርመን የምትባል ሀገር የሌለችበት ነገር ግን ኢትዮጵያ የምትገኝበትን አንድ ካርታ ላከላት ከዚያን ጊዜ በኋላ አልተጻጻፉም ዘጋችው ነው የሚባለው ጥርቅም አድርጋ፡፡
ዛሬ እሷን ሆኜ ሳስበው ታሪካቸው ከኛ ሀገር ታሪክ እኩል ባለመሆኑ ተናዳ ተባሳጭታ ወይም አፍራ መሆን አለበት፡፡
በእንድ ወቅት እግዚአብሔር ከእስራኤል ጋር ቃል ኪዳን በገባበት የቃሌ ኪዳን ታቦት እጅግ ታላላቅ ተአምራትን ያደረገና ይህ በአንድ ወቅት የዓለምን ታሪክ ይመራ የነበረ የቃሌ ኪዳን ታቦት የት እንደሚገኝ የማይታወቅና ያልተረጋገጠ ነው ብለው የሚያምኑ ሀያላን ሀገራት የዚህ ታላቅ ታሪክ እና ቅርስ ባለቤት ለመሆን ዓለምን ሲንጧት እያየን ብዙ ታዝበናል፡፡ ምናልባትም በሀገራችን የጽላት ሽያጭ ለታሪክና ቅርስ ግድ የሌላቸው እና ሆዳቸው አምላካቸው የሆኑ ሰዎችን ተገን በማድረግ በሚደንቅ እና መጠኑ በበዛ ገንዘብ እየተቸበቸበ ያለው ምናልባትም የሙሴ ጽላትን ብናገኝ ብለው እንደሆነ ይታመናል፡፡
ይኽ ሁሉ ሰው ለታሪክ ለሀገርና ለቅርስ ያለውን ስሜት የሚናገር ይመስለኛል፡፡ ሀገርን ታሪክን እና ቅርስን ለመውደድና ለማክበር ምክንያት የሚያስፈልግ አይመስለኝም፡፡
አሁን አሁን ግን የምናያቸው ነገሮች ከዚህ እየወጡ ይመስለኛል፡፡ ትቅልዱ ለታሪኩና ለቅርሱ ግድ እንዳይኖረው የሚሰብኩ ብዙዎች ናቸው፡፡ መንግስትም እንደመንግስት ሰው ለሀገሩ ለቅርሱና ለታሪኩ ግድ እንዲኖረው የሚጠበቅበትን ሁሉ እየሰራ ነው የሚል እምነት የለኝም፡፡ በትምህርት ቤት በዩንቨርሲቲዎች ጭምር የታሪክ ትምህርት ከየ ካሪኩለሙ እየሳሳና እየወጣ ይመስለኛል በአንዳንድ የግል ትምህርት ቤቶች አማርኛ መናገር የወንጀል ያክል እየታየ መምጣቱ የአደባባይ ምስጢር እየሆነ ነው፡፡ ለሀገር ለታክና ለቅርስ ለሃይማኖትም ግድ የሌለውን ትውልድ ሀገር እያፈራች እና እያሳደገች ይመስለኛል፡፡
ወገኔ ስለ ወንጭፍ ወይም ቀስት አስበህ ታውቃለህ ወንጭፍም ሆነ ቀስት ሩቅ የሚሄደው ወደ ኋላ በሚሳበው መጠን ነው፡፡ እድገት ብልጽግናም ዘመናዊነትም እንደዚሁ ይመስሉኛል፡፡ ታሪክን ወደ ኋላ ባየንው በቃኘነው ቁጥር ይመስለኛል ወደ ፊት በሚገባው ፍጥነት መወንጨፍ የምንችለው፡፡ ‹‹የኋላው ከሌለ የለም የፊቱ›› ይባል የለ፡፡
ሕብረተሰቡ በቀና ጎዳና እንዲራመድ ከሚያግዙና ከሚያስተምሩ መንገዶች፣ መድረኮች ወይም ተቋማት መካከል የኪነጥበቡ መድረክ አንዱ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ አሁን በቴዎድሮስ ትዝታ ቴያትር እንዳየሁት አዘጋጁን አደንቃለሁ የጋዙኝን አመሰግናለሁ፡፡
መስመሬ ስላልሆነ በጥልቀት መንካት ባልፈልግም ፊልሞቻችንም ይህንን አርአያ ቢከተሉ እንዴት መልካም ነበር ማለት እፈልጋለሁ፡፡
ብዙ በታሪክ ላይ የሚያጠነጥኑ ፊልሞችን ሳይ እኛ ታሪክ የለንም ወይስ ታሪክን በፊልም መልክ መስራት ለኛ አልተፈቀደም ብዬ እንዳስብ ያደረገኘ ጊዜ አንዴና ሁለት ግዜ ብቻ አይደለም፡፡ አሁን በእኛ ሀገር በቀን አንድ ፊልም መውጣት ጀምሯል የሚል ነገር እንዳነበብኩ አስታውሳለሁ፡፡ ግን ታሪክን የሚያስተምር የሚያሳይ ፊልም ግን እንዳለ መስማቴን እጠራጠራለሁ፡፡ ብዙዎቹ እሁድ በተቀረጹበት ልብስ ሰኞ ካፌ የሚታዩ ቤት ለምነው የሚቀረጹ አሁን ያለንበትን አኗኗር ብቻ የሚያሳዩ መሆናቸውን ሳይ ወደ ኋላ ተመልሰው ፊልም ለመስራት በጊዜው የነበረውን ገጽታ ለመሳል የሚቻልባቸውን ነገሮች ለማዘጋጀት እና ለፊልሙ የሚሆን መንደር ለመገንባት ወጪ ማውጣት የሚፈሩ ወይም የማይፈልጉ ይመስለኛል፡፡
ተመልካች አናገኝም ብለው እንዳይሆን ግን የቴዎድሮስ ትዝታን ተጋፍቶ ከሁለት ሰዓት በፊት ቀድሞ የሚገኝ ተመልካች ሀሳባቸውን ያፈርሰዋል፡፡
ለሀገሩ ለታኩና ለቅርሱ የሚጨነው ትውልድ ፈጣሪ አያሳጣን
ይብቃኝ በድጋሜ በማየቴ ተደስቻለሁ አዘጋጁን አከብራሉ የጋበዙኝን አመሰግናለሁ ያላያችሁትን ጋዣለሁ ሠላም